Tuesday, July 23, 2013

የዩናይትድ ስቴትስ የስለላ ቅሌትና መዘዙ



የዩናይትድ ስቴትስ የስለላ ቅሌትና መዘዙ

ሥለ NSA የተለያዩ መፅሐፍት ያሳተመዉ ጋዜጠኛ ጀምስ ባምፎርድ እንደሚለዉ፥ እርስዎ ከዱባይ ወይ ከለንደን አዲስ አበባ ላለች ፍቅረኛዎ የፍቅር ኢሜል ይመይላሉ እንበል።ስኖዳን እና ብጤዎቻቸዉ ሐዋይ፥ ሜሪላንድ ወይም የፈለጉበት ቦታ ሆነዉ-ከፍቅረኛዎ እኩል ምናልባትም ቀድመዉ ኢሜልዎን ያነባሉ።ስልኩም---
የትንሹ ሠላይ ትልቅ ድፍረት፥ የትልቂቱ ሐገር ታላቅ ቅሌት።የልዕለ ሐያሊቱ ሐገር የሥለላ ቅሌት መነሻ፥አስተጋብኦቱ ማጣቀሻ፥ ያስከተለዉ ዉዝግብ መድረሻችን ነዉ-ላፍታ አብራችሁን ቆዩ።
የመረጃ ሰዎች ካንዱ መንግሥት ወደ ሌላዉ መኮብለል፥ ወይም መንግሥታት የተቀናቃኛቸዉን መንግሥት ሰላይ ማስኮብለል እንግዳ አይደለም።በቀዝቃዛዉ ጦርነት ወቅት በሞስኮ ዋሽግተኖች የሚተወን የዉሎ አምሽቶ ድራማ አይነት ነበር።

በፕሪስተን ዩኒቨርስቲ የዓለም አቀፍ ሕግ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፋልክ አንዱን ያስታዉሳሉ።ሉዊስ ፖሳዳ ካሪለስ ዛሬ የሰማንያ አምስት አመት አዛዉንት ናቸዉ።የካሊፎርኒያ ነዋሪ፥ ኩባዊ፥ ቬኑዙዋላዊ አሜሪካዊ ናቸዉ።ድሮ-በተማሪነቱ በእድሜ አንድ ዓመት የሚበልጠዉ የፊደል ካስትሮ ወዳጅ ብጤ ነበር።ኋላ ጠላት ሆኑ።

በ1963 (ዘመኑ በመሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) የአሜሪካዉ ማዕከላዊ የሥለላ ድርጅት (CIA በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ) የማሸበር፥ የመግደልና የመሻጠር ሙያ አሰለጠነዉ።ከእንግዲሕ አንቱ ናቸዉ።ፖሳዶ ካስትሮን ለመግደልና ለማስገደል በተደጋጋሚ ሞክሩ።በተፈጥሮ ያዳበሩት ድፍረት፥ ጥላጫ፥ ከአሜሪካኖች የቀሰሙት ዕዉቀት፥ መሳሪያ ገንዘብም ብዙ አልፈየዳቸዉም።ሰዉዬዉ አልተገኙም።ፖሳዳም ደም-ለማፍሰስ ማድባታቸዉን አልተዉም።

A protester wearing a Guy Fawkes mask holds a paper-made mock TV camera during a demonstration against the National Security Agency (NSA) and in support of U.S. whistleblower Edward Snowden, outside the Dagger Complex, which is used by the U.S. Army intelligence services, in Griesheim, 20 km (12.4 miles) south of Frankfurt, July 20, 2013. REUTERS/ Kai Pfaffenbach (GERMANY - Tags: POLITICS CIVIL UNREST CRIME LAW TPX IMAGES OF THE DAY) የሥለላዉን ድርጅት በመቃወም


1976 ሰላዩ ለካስትሮና ለተከታዮቻቸዉ ያነጣጠሩትን የጥፋት ለበቅ ተራ-ወገኖቻቸዉ ላይ ሊያወርዱት ወሰኑ።የበረራ ቁጥር 455 ፥ የኩባ የመንገደኞች አዉሮፕላን ወደ ኪንግሰቶን-ጃማይካ ሊበር ከባርቤዶስ አዉሮፕላን ማረፊያ ተነሳ።ብዙም አልቆየ።ጋየ።ሰባ-ሁለት መንገደኞቹም ከሰሉ።

የየዋሕ መንገደኞች ቤተሰቦች፥ ዘመድ፥ ወዳጆች፥ ሲላቀሱ፥የብዙዉ ዓለም መንግሥታት ሽብሩን ሲያወግዙ የሲ አይ ኤዉ ጀግና ተደሰቱ።ዩናይትድ ስቴትስም አሸባሪ ጀግናዋን እጇን ዘርግታ ተቀበለችዉ።ዘንድሮ በሰላሳ ሰባት ዓመቱ የሰላሳ ዓመቱ አሜሪካዊ ሰላይ ኤድዋርድ ስኖደን ከሐዋይ በሆንግ ኮንግ አድርጎ ሞስኮ ገባ።

ስኖደን አንድም ሰዉ አልገደለም።ለመግደልም አልሞከረም።ገንዘብ አልዘረፈም።ለመዝረፍም አልሞከረም።የታላቂቱን ሐገር ትልቅ ደባና ሚስጥር ግን በርግጥ አጋለጠ።እና ፖሳዳና ብጤዎችን አሸባሪዎች የምትንከባከበዉ፥ትልቅ ሐገር ትንሹን የቀድሞ ሰላይዋን ለመያዝ በትላልቅ ጥፍር ጥርሶቻ መንግሥታትን ትቧጭር፥ ትናከስ ያዘች።

«እኔ አሁንም የምጠብቀዉ ሩሲያም ሆነች፥ ሌሎች ለሚስተር ስኖደን፥ ጥገኝነት ለመስጠት እንፈልጋለን የሚሉ ሐገራት የዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ አካል መሆናቸዉን ይገነዘባሉ፥እና ለዓለም አቀፉ ሕግ መገዛት አለባቸዉ ብዬ ነዉ።»

ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ፥ ዓለም አቀፍ ሕግ ትርጉም ብያኔ እንዴትነት ሁሌም እንዳወዛገበ፥ እንዳነጋገረ በጉልበተኞች ልክ የሚሰፋ-ወይም የሚጠብ ነዉ።የድፍን ዓለም ማሕበራት፥ የዜጎች፥ የፖለቲከኞች፥ የሙሕሯን፥ የጋዜጠኞችን፥ የደራሲዎችን፥ የጦር መኮንኖች ወዘተ የስልክ ንግግር፥ የኢሜይል ልዉዉጥ፥ ባንዲት ሐገር እንዲቀዳ፥ እንዲከማች፥ ለተፈለገ ወገን እንዲሰጥ የፈቀደ ዓለም አቀፍ ሕግ፥ ዓለም አቀፍ ማሕበረሰብስ ካለም ዓለም አቀፉ ጉልበት፥ ሐብት፥ ወይም ለሕግ አለመገዛት መሆን አለበት።

ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ፍፃሜ በሕዋላ የዓለምን የልዕለ-ሐይልነት ጉልበት ጠቅላላ የያዘችዉ ዩናይትድ ስቴትስ እንደ ጦር ጉልበቷ፥ እንደ ሐብቷ ሁሉ በስለላዉም የሚስተካከላት የለም።NSA በሚል ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ ብሔራዊ የፀጥታ ድርጅት ሠላሳ አምስት ሺሕ ቋሚ ሠራተኞች አሉት።


Bildnummer: 59982415 Datum: 03.07.2013 Copyright: imago/Christian Ohde
Kopfhörer mit USA-Fahne auf einem Tisch, Symbolfoto Abhörskandal Prism Symbolfoto Abhörskandal USA xcb x0x 2013 quer Abhörprogramm Abhörprogramme Computerprogramm Computerprogramme Datensammlung Kontrolle NSA Prism Spionage Spionageprogramm Spionageprogramme Spähprogramm Spähprogramme Symbolbild Symbolbilder Symbolfoto Symbolfotos ausspähen kontrollieren online spionieren von Späh-Skandal Spähaktion Spähaktionen Abhörskandal Abhörskandale Abhör-Skandal abhören Kopfhörer mithören Zahlencode binär binärer Binärcode USA-Fahne US-Fahne Fahne Flagge 
59982415 Date 03 07 2013 Copyright Imago Christian Ohde Headphones with USA Flag on a Table Symbolic image Wiretapping scandal Prism Symbolic image Wiretapping scandal USA x0x 2013 horizontal Computer program Computer programs Data collection Control NSA Prism Espionage Symbol image Symbol Pictures Symbolic image Icon photos Spying control Online Spy from Scandal Wiretapping scandal Interception Scandal Interception Headphones Listening Numeric code binary binary Binary code USA Flag U.S. Flag Flag Flag የሥልክ ጠለፋ ምሳሌ
የስኖደን ብጤ የኮንትራት ሠራተኞች ቁጥር ከቋሚዎቹ አይተናነስም።ሥለ NSA የተለያዩ መፅሐፍት ያሳተመዉ ጋዜጠኛ ጀምስ ባምፎርድ እንደሚለዉ፥ እርስዎ ከዱባይ ወይ ከለንደን አዲስ አበባ ላለች ፍቅረኛዎ የፍቅር ኢሜል ይመይላሉ እንበል።ስኖዳን እና ብጤዎቻቸዉ ሐዋይ፥ ሜሪላንድ ወይም የፈለጉበት ቦታ ሆነዉ-ከፍቅረኛዎ እኩል ምናልባትም ቀድመዉ ኢሜልዎን ያነባሉ።
«በኢንተርነት የሚደረገዉ ከዘጠና ዘጠኝ በመቶ በላይ ግንኙነት አንድም ወደ አሜሪካ ይገባል አለያም በአሜሪካ በኩል ያልፋል።ሥለዚሕ ዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ አቅም አላት።መቼም እንዲሕ አይነቱን አቅም ኔዘርላንድስ ወይም ሌላ የአዉሮጳ ሐገር ይኖረዋል ብለሕ አትጠብቅም።»

ሥልክ የደዉሉት ከጂዳ፥ የተደወለልዎት ካፓርስ ነዉ እንበል።ወዴትም ይደዉሉ፥ ከየትም ይደወልዎት ከሰማንያ ከመቶ የሚበልጠዉ የሥልክ ንግግር በአሜሪካ በኩል ነዉ የሚያልፈዉ።

«በስልክ ንግግርም ቢሆን ከሰማንያ በመቶ የሚበልጠዉ በአሜሪካ በኩል ነዉ የሚተላለፈዉ።ሥለዚሕ ዩናይትድ ስቴትስ የዓለምን ግንኙነት ለመምጠጥ ከፍተኛ ዕድል አላት።»

አሜሪካን ሳይነካ የሚያልፈዉን የሥልክ ጥሪ እነ ስኖደን ከያለበት ጠላልፈዉ፥ ለቃቅመዉ ከዚያ የመረጃ ትልቅ ጎተራቸዉ ያክቱታል።ከዚያ እያስተረጎሙ፥ እያስተነተኑ ለአለቆቃቸዉ ያቀርባሉ። እርስዎ ተራ ሰዉ ነዎት።በNSA አይን ግን የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክልም ከርስዎ መለየታቸዉን እራሳቸዉ እንዳሉት እርግጠኛ አይደሉም።

Bildbeschreibungen: Bei seinem ersten öffentlichen Auftritt traf sich Edward Snowden am Freitag, den 12 Juli 2013 auf dem Moskauer Flughafen Scheremetjewo mit Menschenrechtlern und Anwälten. Der US-Amerikaner möchte in Russland bleiben, solange er nicht nach Südamerika ausreisen kann.
Menschenrechtsbeauftragter der RF Wladimir Lukin inmitten der Journalisten.
Foto: Jegor Winogradow / DW ስኖደን ከመብት ተሟጋቾች ጋር


«እኔ እራሴ የሥልክ ንግግሬ የት እንደተቀዳ አላዉቅም።ባዉቅ ኖሩ ለፓርላማዉ ኮሚቴ አናገር ነገር።»

ለዩናይትድ ስቴትስ ኢራን፥ ሶሪያ፥ ቬኑዙዌላ፥ ቦልቪያ፥ ኢኳዶር የቅርብ ክትትል የማይለያቸዉ «ጠላቶች» ናቸዉ።ብራዚል «ወዳጅ» ናት።ከካራካስ ባለሥልጣናት፥ እኩል የብራዚሊያ ሹማምንት፥ ከቦሊቢያ ዜጎች እኩል የብራዚሎች ንግግር፥ ፅሁፍ፥ እየተጠለፈ፥ እንቅስቃሴያቸዉ እየተቀዳ ይጠራቀማል።

ለዋሽግተኖች፥ ሞስኮዎች ወይም ቤጂንጎች የቀዝቃዛዉ ጦርነት ዘመን ጠላት ናቸዉ።አሁን ደግሞ በተለይ ቻይና የምጣኔ ሐብት ተፎካካሪ፥ የዓለም አቀፍ መርሕ ተፃፃራሪ ናት።የጆርጅ ደብሊዉ ቡሽ መስተዳድር የባግዳድን ቤተ-መንግሥት ያስረከባቸዉ የኢራቅ የሺዓ ፖለቲከኞች አፍ-አይ’ናቸዉ ከአዋሽግተኖች፥ ልብ ቀልባቸዉ ደግሞ ከቴሕራኖች ጋር ነዉ ይባላል።ለክፉዉም ለደጉም በቅጡ መሰለል አለባቸዉ።

ጀርመን ባንፃሩ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት አባል፥የዩናይትድ ስቴትስ የቅርብ ተሻራኪ ጥብቅ ወዳጅ ናት።ግን ስኖደን ያጋለጠዉ መረጃ እንዳመለከተዉ ጀርመኖች ከቻይኖች እና ከኢራቆች እኩል ይመረጃሉ።ለጀርመኖች በርግጥ አስደንጋጭ ነዉ።ጋዜጠኛና የስለላ መፅሐፍት ደራሲዉ ጄምስ ባምፎርድ እንደሚለዉ አሜሪካኖች ጀርመን ላይ የጨከኑት ጀርመኖች የአሜሪካ «ጠላት» ሥለሆኑ አይደለም ባይ ነዉ።

«ጀርመን በብዙ ምክንያት የአሜሪካንን ትኩረት ትስባለች።አንደኛዉ ምጣኔ ሐብታዊ ነዉ።ጀርመን የአዉሮጳ የምጣኔ ሐብት ዋና ማዕከል ናት።ሁለተኛዉ የመስከረም አንዱ የአሸባሪዎች ጥቃት የተጀመረዉ ከጀርመን ነዉ።ሰወስተኛዉ ጀርመን አዉሮጳ ዉስጥ ምጣኔ ሐብታዊ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ ተፅዕኖም ታሳርፋለች።ሥለዚሕ የጀርመንን ንግግር ማድመጥ ማለት የኔዘርላንድስ፥ የስጳኝ፥ የግሪክ የሌሎችንም የአዉሮጳ ሐገራት እንቅስቃሴን በዚሕ በሚስጥር መገናኛ ዘዴ አማካይነት ማወቅ ማለት ነዉ።»

ጀርመኖችን በመሠለሉ ሒደት የጀርመን መንግሥት ባለሥልጣናት በተለይም የሐገሪቱ ፌደራላዊ የሥለላ ድርጅት (ቡንደስ ናኽሪሽተን ዲኒስት) መሪዎች ከአሜሪካኖች ጋር ተባብረዋል የሚለዉ ዘገባ የጀርመን ፖለቲከኞችን እያወዛገበ ነዉ።የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች የሥለላዉ ተቋም ባለሥልጣናት ከሥልጣን መዉረድ አለባቸዉ እስከማለት ደርሰዋልም።

የአገር አስተዳደር ሚንስትር ሐንስ ፔተር ፍሬድሪሽ አሜሪካኖች ጀርመንን ሥለመሠለላቸዉ ማብራሪያ እንዲሰጧቸዉ ዋሽግተን ድረስ ሔደዉ ጠይቀዉ ነበር።የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ጥያቄና ጥርጣሬ የሚያስወግድ መልስ ግን አልሰጡም።ወይም አላገኙም።መራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክልም የአሜሪካ ሠላዮች የጀርመንን ሕግ ሥለ መጣስ-አለመጣሳቸዉ የማዉቀዉ ነገር የለም ባይ ናቸዉ።


Barack Obama telefoniert im Oval Office
picture alliance / Photoshot ኦባማ
«የጀርመንን ሕግ አለማክበራቸዉን የሚያረጋግጥ መረጃ የለኝም።ባለሙያዎቻችን ይሕን ጉዳይ እንዲያጣሩ ለነሱ እንተወዋለን።ባስቸኳይ መታወቅ አለበት።በዚሕ ሒደት የአገር አስተዳደር ሚንስትሩና የምክር ቤቱ ልዩ ኮሚቴ የሚያጠናክሩትን ዘገባ ካየን በኋላ መወሰድ ሥላለበት ጉዳይ እናጤናለን።ለወደፊቱ ግን በምንም መንገድ የጀርመን ሕግ መጠበቅ አለበት።»
ጀርመኖችን ከጀርመኖች የሚያጨቃጭቀዉ የሥለላ ቅሌት አሜሪካኖችን ከሩሲያዎች፥ ጋር እያወዛገበ ነዉ።የፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ቃል አቀባይ ጄ ካርኒ ልክ እንደ ኦባማ ሁሉ ሩሲያ የቀድሞዉን አሜሪካዊ ሠላይ ለአሜሪካ አሳልፋ መስጠት አለባት ይላሉ።

«ከቦስተኑ ማራቶን የቦምብ ጥቃት በኋላ ከሩሲያ ጋር ያለንን የተጠናከረ ትብብር ከግምት በማስገባት እና በሩሲያ ጠያቂነት ከፍተኛ ወንጀል የፈፀሙ ሰዎችን አሳልፈን መስጠታችንን ጨምሮ፥ ሕግን በማስከበሩ መስክ ለረጅም ጊዜ ካለን ትብብር አኳያ የሩሲያ መንግሥት ሚስተር ስኖደንን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ያባርራሉ ብለን እንጠብቃለን።»

የቦሊቪያዉ ፕሬዝዳት ኢቮ ሞራሌስ ሞስኮ የገቡት ሞስኮ-ዋሽግተኖች ጠጣር ቃላት ሲወራወሩ ነበር።ድፍን ዓለምን የሚሰልለዉ የልዕለ-ሐያሊቱ ሐገር ግዙፍ የሠላላ ባለሙያዎች ፕሬዝዳት ሞራሌስ ታዳኙን ሠላይ ኤድዋርድ ስኖደንን ባዉሮፕላናቸዉ ይዘዉ ወደ ሐገራቸዉ ሊመለሱ ነዉ አሉ።የዩናይትድ ስቴትስን ቁጣና ግልምጫ የሚፈሩት የፈረንሳይ፥ የስጳኝ፥ የፖርቱጋልና የኢጣሊያ መንግሥታት የሞራሌስ አዉሮፕላን በአየር ክልላቸዉ እንዳይበር አገዱ።

የኦስትሪያ ባለሥልጣናት አዉሮፕላኑን አሳርፈዉ ፈተሹ።ሶኖደን አልነበረም።የደቡብ አሜሪካ መንግሥታት እንደ ብዙዉ ዓለም መንግሥታት በአሜሪካ በመሠለላቸዉ ኦባማ «ዓለም አቀፍ» በሚሉት ሕግ መሠረት እንክሰስ አላሉም። ቢሉም የሚሰማቸዉ የለም። ከፕሬዝዳንታቸዉ አንዱ በሐሰት መረጃ ለአዉሮፕላን አደጋ መጋለጣቸዉን ግን አልታገሱትም።አወገዙት።

ቁጣ ዉግዘቱ ግን ከአፍታ የመገናኛ ዘዴዎች ዜናነት አላለፈም።የፕሬዝዳት ቭላድሚር ፑቲን አፀፋ እንደ ጀርመኖች-በአገም ጠቀም፥ እንደደካማዎቹ የደቡብ አሜሪካ ሐገራት ባፍታ ቁጣ የሚያበቃ አይነት አይደለም።

«እኛ እንደሌሎች መንግሥታት አናጎበድድም።ሩሲያ የራስዋ ነፃ የዉጪ መርሕ አላት።ይሕ መርሐም በዚሁ ይቀጥላል።ወዳጆቻችን ይሕን አጢነዉ አደብ ቢገዙ ጥሩ ነዉ።ከሥለላ ዉዝግብ ይልቅ የአሜሪካና የሩሲያ ግንኙነት በጣም አስፈላጊ ነዉ።»

Russian Prime Minister Vladimir Putin visits the Far Eastern State University in Vladivostok, about 9,300 kilometers (some 5,750 miles) east of Moscow, on Monday, Sept. 1, 2008. A portrait of Czar Nicholas II is at left. (AP Photo/ RIA Novosti, Alexei Druzhinin, Pool ) ፑቲን


አሜሪካኖች ግን አላረፉም።በመጪዉ ነሐሴ ማብቂያ ሩሲያ በምታስተናግደዉ የቡድን ሃያ አባል ሐገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ፕሬዝዳት ኦባማ እንዳይካፈሉ ወግ አጥባቂዎቹ የአሜሪካ ፖለቲከኞች እየጎተጎቱ ነዉ።ቬኑዙዌላ፥ የኢኳዶር እና የቦሊቪያ መንግሥታት ሞስኮ አዉሮፕላን ማረፊያ «ለታገተዉ» የቀድሞ የአሜሪካ ሠላይ ጥገኝነት ለመስጠት በመፍቀዳቸዉ ከዋሽግተን የሚሰነዝርባቸዉ የቅጣት ዛቻ፥ ማስፈራሪያም እንደቀጠለ ነዉ።እኛ ለዛሬዉ ከዚሕ በላይ መቀጠል አንችልም።ነጋሽ መሐመድ ቸር ያሰማን።

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

source....http://www.dw.de

Friday, July 19, 2013

በወልዲያ ከተማ ሰላም መስጂድ

በወልዲያ ከተማ ሰላም መስጂድ ለጁምአ ሰላት የተገኙ በርካታ ሙስሊሞች በፖሊስ ከበባ ውስጥ ናቸው፡፡ አሁን ከአካባቢው በደረሰን መረጃ የጁምአ ሰላት እንደተጠናቀቀ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ጥይት በመተኮስ ወደ መስጂዱ ቅፅር ጊቢና ወደ ዋናው መስገጃ ክፍል በመግባት በርካታ ወጣቶችን ያገቱ ሲሆን አርጋውያን የሆኑትን መስጂዱን ለቀው ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ አስገድደዋቸዋል፡፡ ፌዴራል ፖሊሶች የመስጂዱን በሮችና መስኮቶች በሀይል መስበራቸውም ተነግሯል፡፡ በሴቶች በኩልም በተመሳሳይ ወደ 18 የሚጠጉ ሙስሊም እህቶቻችንን አፍነው መውሰዳቸው ተረጋግጧል፡፡ በወንዶች በኩል አሁንም ፌዴራል ፖሊሶች መስጂዱን ከበው ከውስጥ ያገቷቸውን ሙስሊሞች ምን እያደረጓቸው እንደሆነ በውል ማወቅ አልተቻለም፡፡ ከአካባቢው ሰዉ እንዲርቅም ፖሊሶች እያስገደዱ ነው፡፡ ሰው ከመስጂዱ መውጣትም መስጂዱ ውስጥ መቀመጥም አልቻለም፡፡
 
 
 
source....miniliksalisawi

ዓረና ትግራይ ፓርቲ በመቐለ ህዝባዊ ስብሰባ ጠራ

ዓረና ትግራይ ፓርቲ በመቐለ ህዝባዊ ስብሰባ ጠራ


ፓርቲው ለእሁድ ሓምሌ 14, 2005 ዓም በመቐለ ማዘጋጃቤት አዳራሽ ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱ ተሰምቷል። ፓርቲው ‘አሉ’ በሚላቸው የህዝብ ችግሮች (ኑሮ ውድነት፣ የወጣቶች ስደት፣ የግብር አከፋፈል ችግሮችና የሙስና ሁኔታ፣ የመልካም አስተዳደር እጦትና የመሳሰሉት የህዝብ ችግሮችና በዓረና ትግራይ የሚቀርቡ አማራጭ መፍትሔ ሓሳቦች ከመቐለና አከባቢው ህዝብ ነዋሪዎች መወያየት እንደሚፈልግ አስታውቋል። ሁላችን ተጋብዘናል፤ እንሳተፋለን።
ስንሳተፍ ግን ምን እንጠብቃለን? ዓረናዎች የህዝብ ችግሮችና የመፍትሔ አማራጫቸውን ሲነግሩን የህወሓት ደጋፊዎች (መሳተፋቸው አይቀርም ከሚል ነው) ደግሞ ‘ እናንተ ዓረናዎች እኮ ያው ናችሁ። ህወሓት ነበራቹ። ያኔ ለውጥ አላመጣችሁም።’ የሚል የተለመደ የፕሮፓጋንዳ ስትራተጂ መጠቀማቸው አይቀርም።
እኔም እላቸዋለሁ፡ አዎ! አብዛኛው የትግራይ ህዝብ የህወሓት ታጋይ ነበር፤ የህወሓት ፓርቲ አመራር አባል ግን አልነበረም። እነኚህ የዓረና አባላትም የትግራይ ህዝብ አባላት እስከሆኑ ድረስ የህወሓት ታጋዮች ነበሩ። የህወሓት ታጋይ መሆን በራሱ ስሕተት አይደለም። ህወሓት እንደ ትግልና እንደ ገዢ መደብ የተለያዩ ናቸው።
ግን ደግሞ የህወሓት ደጋፊዎች (አብዛኞቹ የህወሓት አባላት) ዓረናዎችና ህወሓቶች ‘ያው አንድ’ መሆናቸው የሚያምኑ ከሆነ ለህወሓት የሚሰጡትን ድጋፍ ለዓረናም መስጠት አለባቸው ማለት ነው፤ ምክንያቱም ‘ያው አንድ’ አይደሉም እንዴ? በአንድ በኩል ‘ዓረናና ህወሓት ያው ናቸው፤ አብረው ነበሩ። ስለዚህ ዓረና ፓርቲ ከህወሓት የተለየ ለውጥ ሊያመጣ አይችልም’ ብለው ይከራከራሉ። በሌላ በኩል ደግሞ ዓረና ትግራይ ፓርቲን በጠላትነት በመፈረጅ ህወሓትን የሚቃወም ሰው ፀረ የትግራይ ህዝብ ትግል አስመስለው ያቀርባሉ።
አዎ! እነኚህ ዓረናዎች የህወሓት ታጋዮች ነበሩ። የህወሓት የአመራር አባላት የነበሩ የዓረና ትግራይ አባላት ግን በቁጥር ሦስት ብቻ ናቸው። አንደኛ እነዚህ ሦስት ሰዎች ከህወሓት አመራርነት ወደ ዓረና አመራርነት ስለተቀየሩ ዓረናና ህወሓት ‘ያው አንድ’ ናቸው ሊያስብል አይችልም፤ ምክንያቱም የዓረና አባላት ሦስት ብቻ አይደሉም።
ሁለተኛ እነኚህ ሦስት ሰዎች (ወይም ማንኛውም ሰው) ህወሓት ወይ ዓረና ወይ ሌላ የሚያደርጋቸው የፖለቲካ አስተሳሰባቸው (አመለካከታቸው) ነው። ሦስቱ የአመራር አባላት ከህወሓቶች ‘ያው አንድ’ ቢሆኑ ኑሮ ለምን ህወሓትን ለቀው ወጡ? ከፍተኛ ባለስልጣናት አልነበሩምን? ለምን ስልጣናቸውን ጠብቀው ‘ተከብረው’ አልኖሩም? ከህወሓቶች ያው ቢሆኑ ኑሮ ለምን በህወሓት መሪዎች ይሰደባሉ? ይዋረዳሉ? ይታሰራሉ?
በአንድ በኩል ‘ህወሓት የነበሩ ናቸው፣ በስልጣን በነበሩበት ግዜ ለውጥ አላመጡም’ ይባላል። በሌላ በኩል ደግሞ ‘ሰዎቹ ዓረና የሚል የተቃዋሚ ፓርቲ የመሰረቱት ስልጣን ፈልገው ነው’ የሚል የመከራከርያ ነጥብ አለ። ሁለቱም ነጥቦች እርስበርሳቸው ይጣረሳሉ። የህወሓት አመራር አባላት በነበሩበት ግዜ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከነበሩ እንዴት ስልጣን ፈልገው ከህወሓት ወተው ሌላ ፓርቲ መሰረቱ ሊባል ይችላል? የስልጣን ጥማት ቢኖራቸው ኑሮ እንደ አንዳንዶቹ ‘ይቅርታ’ ጠይቀው ወደ ፓርቲው ተመልሰው ገብተው ስልጣን አይዙም ነበር?
‘ከህወሓት ጋር አብረው በሰሩበት ግዜ ለውጥ አላመጡም’ በሚል ሓሳብ ግን እስማማለሁ። አዎ! ተገቢውን ለውጥ አላመጡም። ነገር ግን በህወሓት የፖለቲካ ስትራተጂ መሰረት ለውጥ ወይ ውድቀት የሚያመጣው ግለሰብ ሳይሆን ድርጅቱ እንደስርዓት ነው። የህወሓት የፖለቲካ አሰራር ‘ዴሞክራቲክ ሴንትራሊዝም’ ነው። በ‘የተማእከለ ዴሞክራሲ’ (Democratic Centralism) እሳቤ መሰረት ማንኛውም የፓርቲው አባል (ወይ አባላት) ድርጅቱን የሚቃወም ሓሳብ ማራመድ አይችልም። የፓርቲው አሰራር መተቸት የሚቻለው በድርጅቱ ውስጣዊ ግምገማ ብቻ ነው። ተቃውሞውን ለህዝብ ይፋ ከሆነ የተቃወመውን ሰው ከድርጅቱ ይባረራል።
እነኚህ ከህወሓት የለቀቁ የአመራር አባላት ተቃውሟቸውን ሲገልፁ ቆይተዋል። ግን ለህዝብ ይፋ አልሆነም ነበር። በመጨረሻ ግን ከዓቅም በላይ ተወጥሮ ፈነዳ። መቃወማቸው ታወቀ። እንደዉጤቱም ፓርቲው ለቀው ወጡ። በዴሞክራቲክ ሴንትራሊዝም አመራር አባላት የማይደግፉትን አሰራር ጭምር እንዲተገብሩ ይገደዳሉ። የማያምኑበትን አሰራር ለመተግበር ሲገደዱ በስራቸው ዉጤታማ ላይሆኑ ይችላሉ። በህወሓት የፖለቲካ አሰራር መሰረት ለውጥ የሚያመጡ ወይ የማያመጡ ግለሰቦች ሳይሆኑ ድርጅታዊ ስርዓቱ ነው (የግለሰቦች ሚና የማይናቅ ቢሆንም)። እናም ህወሓትን የምንቃወመው ስርዓቱን እንጂ ግለሰቦችን አይደለም።
ስለዚህ የዓረና አመራሮች በህወሓት እያሉ ተገቢውን ለውጥ ስላላመጡ አሁንም (በዓረና ፓርቲ) ለውጥ ሊያመጡ አይችሉም የሚል ድምዳሜ ትክክል አይመስለኝም። ምክንያቱም ሰዎቹ ‘ያው’ ቢሆኑ እንኳን የስርዓቱ አሰራር የተለያየ ነው (ወይም ተቀይሯል)። የህወሓትና የዓረና የፖለቲካ አሰራር የተለያየ ነው፣ በዓረና ፓርቲ ዴሞክራቲክ ሴንትራሊዝም አይሰራም። ዓረና ለውጥ ሊያመጣ ይችላል።
ህወሓት እየተከተለው ያለው የፖለቲካ ፍክክር ስትራተጂ ጤናማ አይደለም። የዓረና አመራሮች ያው ህወሓት የነበሩ ናቸው ካልን የህወሓት አባል የነበረ ሁሉ ከሌላ ፓርቲ ጋር መቀላቀል አይችልም ማለት ነው? (ይህን አቅጣጫ የራሳቸው የህወሓት አባላትን ፖለቲካ መብት የሚጋፋ ነው።) የህወሓት አባል የሆነ (ወይ የነበረ) ሰው የፈለገውን የፖለቲካ አመለካከት የመያዝ መብት የለውም ማለት ነው? የትግራይ ህዝብ ትግል ለነፃነት ካልሆነ ለሞት ነበር ማለት ነው? የህወሓት ታጋዮች የፈለጉትን ፓርቲ እንዲመሰርቱና እንዲደራጁ ካልተፈቀደላቸው የትግላቸው ውጤት ታድያ ምንድነው? ሌላ ዓፈና? በትግሉ የተሳተፉ ሰዎች እንዲህ መብታቸው ከተነፈጉ በትግሉ ያልተሳተፈ (በግዜ ምክንያት) አዲሱ ትውልድ የመደራጀት መብቱ እንደሚጠበቅለት በምን እርግጠኞች መሆን እንችላለን? ህወሓት ለነ ገብሩ አስራት ያልበጀች ለኔ ትጠቅማለች ብዬ እንዴት ልመን?
የህወሓት መሪዎች ለህዝብ እንደሚሰሩ ይነግሩናል። በተግባር ግን ህዝብ አማራጭ የፖለቲካ ድርጅት እንዳይኖረው ይጥራሉ። በግብፅ የምናየው የፖለቲካ ቀውስ የሙባረክ መንግስት ያጠፋው ጥፋት ውጤት ነው። የሙባረክ መንግስት የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይኖሩ ያደርግ ነበር። አሁን ችግሩን መፍታት የሚችል የተደራጀ ሃይል ጠፋ። ህዝቡ ቀውስ ውስጥ ገባ። ህወሓትም በተመሳሳይ መንገድ እየተራመደ ነው። ህዝብ አማራጭ ፓርቲ እንዳይኖረው የተለያዩ ተፅዕኖዎች እየፈጠረ ‘ከኔ በኋላ ሰርዶ አይብቀል’ እያለን ነው።
ህወሓት ለህዝብ ከቆመ ለምን ህዝቡ እንዲደራጅ አይፈቅድለትም? መደራጀትኮ ሓይል ይፈጥራል (‘ዉዳበ ሓይሊ እዩ!’ እንዶ ይብሉና አይነበሩን ግዲ!)። ህዝብ አማራጭ ፖለቲካዊ ድርጅት ሊኖረው ይገባል።
ዓረና ፓርቲን ስንገመግም ‘አመራር አባላቱ እነማን ነበሩ?’ በሚል መሆን የለበትም። የትናንት አስተሳሰባቸው ስሕተት መሆኑ ተረድተው ሌላ የተሻለ ፖለቲካዊ አመለካከትና አሰራር ይዘው መጥተው ሊሆኑ ይችላሉ (ወይ ላይሆኑ ይችላሉ)። ‘ሌላ የተሻለ አሰራር አላቸው ወይስ የላቸውም ?’ የሚል ጥያቄ ለመመለስ የፖለቲካ ፕሮግራማቸውና ፖሊሲዎቻቸው መመርመር ያስፈልገናል። ለመመርመር ደግሞ ያቀረቡትን አማራጭ ማወቅ ያስፈልገናል። ለማወቅ ደግሞ የፓርቲው ሰዎች ከኛ (ከህዝብ) ጋር የሚገናኙበት መንገድ ሊመቻችላቸው ይገባል። ስለዚህ ህዝባዊ ስብሰባዎች መፈቀዳቸው ጥሩ ነው። አሁን የሚፈለገው የኛ ተሳትፎ ነው። በዚህ መንገድ ዓረና ፓርቲ ጥሩ አማራጭ መሆኑ ወይ አለመሆኑ ህዝቡ ይወስናል።
እስቲ በአደራሹ ተገኝተን የዓረና ትግራይ ፓርቲ አማራጭ ሓሳቦች ምን እንደሆኑ ሰምተን እንገምግም። በዚህ ጉዳይ ከህዝባዊ ስብሰባው በኋላ አስተያየት እሰጥበታለሁ።
የዓረና አማራጭ ሓሳብ ምንም (ጥሩ ወይ መጥፎ) ሊሆን ይችላል። ያም ሁኖ ግን ዓረና ፓርቲ አማራጭነቱ እንደተጠበቀ ነው። የአማራጭ መጥፎ ደግሞ የለም።
ለራሳቸው (ለህወሓቶች)ም ነፃ ልናወጣቸው ይገባል።

በወልድያ 2 ወር ያልሞላትን አራስ ጨምሮ ከ10 ያላነሱ ሙስሊሞች ታሰሩ

በወልድያ 2 ወር ያልሞላትን አራስ ጨምሮ ከ10 ያላነሱ ሙስሊሞች ታሰሩ

576820_643438789017118_1777115518_n
ሐምሌ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዘወትር አርብ የሚደረገውን ስግደት ተከትሎ ተቃውሞ ሊያስነሱ ይችላሉ ተብለው የተጠረጠሩ ከ10 ያላነሱ የወለድያ ከተማ ነዋሪዎች ታስረው ፍርድ ቤት መቅረባቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ተናግረዋል።
ከታሰሩት መካከል ኢብራሂም ገበየሁ፣ ከድር ሙሀመድ፣ ወ/ሮ ሀያት ይማም፣ ወ/ሮ ነሲሳ አህመድ፣ ወ/ሮ ሀያት አህመድ ይገኙበታል። ወ/ሮ ሀያት አህመድ ሁለት ወር ያልሞላት አራስ ስትሆን፣ ወደ እስር ቤት የተወሰደችውም አዲስ ከተወለደው ህጻኗ ተለይታ ነው።
በፖሊስ ጣቢያው አካባቢ የተሰባሰበው ህዝብ ” ቤተሰቦቻችንን ፍቱልን” በማለት ከሰአት በሁዋላ በፖሊስ ጣቢያ አካባቢ በመሰባሰብ ጥያቄ ቢያቀርብም፣ በፖሊስ ተባረዋል።
የአካባቢው ሙስሊሞች “መሄጃ አጣን” በማለት ግራ መጋባታቸውን ተናግረዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የወልድያን ፖሊስ ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።