Friday, July 19, 2013

በወልዲያ ከተማ ሰላም መስጂድ

በወልዲያ ከተማ ሰላም መስጂድ ለጁምአ ሰላት የተገኙ በርካታ ሙስሊሞች በፖሊስ ከበባ ውስጥ ናቸው፡፡ አሁን ከአካባቢው በደረሰን መረጃ የጁምአ ሰላት እንደተጠናቀቀ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ጥይት በመተኮስ ወደ መስጂዱ ቅፅር ጊቢና ወደ ዋናው መስገጃ ክፍል በመግባት በርካታ ወጣቶችን ያገቱ ሲሆን አርጋውያን የሆኑትን መስጂዱን ለቀው ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ አስገድደዋቸዋል፡፡ ፌዴራል ፖሊሶች የመስጂዱን በሮችና መስኮቶች በሀይል መስበራቸውም ተነግሯል፡፡ በሴቶች በኩልም በተመሳሳይ ወደ 18 የሚጠጉ ሙስሊም እህቶቻችንን አፍነው መውሰዳቸው ተረጋግጧል፡፡ በወንዶች በኩል አሁንም ፌዴራል ፖሊሶች መስጂዱን ከበው ከውስጥ ያገቷቸውን ሙስሊሞች ምን እያደረጓቸው እንደሆነ በውል ማወቅ አልተቻለም፡፡ ከአካባቢው ሰዉ እንዲርቅም ፖሊሶች እያስገደዱ ነው፡፡ ሰው ከመስጂዱ መውጣትም መስጂዱ ውስጥ መቀመጥም አልቻለም፡፡
 
 
 
source....miniliksalisawi

No comments:

Post a Comment