Monday, October 14, 2013

ፕሬዝደንታዊ ሚና


ኢትዮጵያ ከደርግ መንግስት በኋላ ሕገ መንግስት ተረቅቆ ከጸደቀ ለሶስተኛ ጊዜ ፕሬዝደንት በያዝነዉ ሳምንት ሰኞ ዕለት ተሰይመዉላታል።
ከደርግ ሥርዓት በኋላ ኢትዮጵያ ተቋቁሞ የነበረዉ የሽግግር መንግስት ፕሬዝደንትን ጨምሮ እስካለፈዉ ሰኞ ድረስ ሶስት ፕሬዝደንቶች ስልጣን ይዘዉባታል። አሁን የምትመራበት ሕገመንግስት ከጸደቀ በኋላ ግን በፕሬደንትነት የተሰየሙት ወይም የተመረጡት ፖለቲከኞች ሶስት ናቸዉ። ሀገሪቱ በምትከተለዉ ፌደራላዊ ፓርላመንታዊ ሥርዓት መሠረት የመራሄ መንግስትነቱ ስልጣን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ነዉ። የሪፐብሊኩ ፕሬዝደንት ስልጣንና ኃላፊነት በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 71 ላይ የተዘረዘረዉ ሲሆን ከዚያ በተረፈ የሀገር ምልክትና ወጋዊ መንበር መሆኑ ይታወቃል። እንዲያም ሆኖ ለስድስት የአገልግሎት ዘመናት የሚሰየመዉ ፕሬዝደንት በሀገሪቱ የፖለቲካና ማኅበራዊ ጉዳዮች ሊኖረዉ የሚገባዉና ኅብረተሰቡ የሚጠብቅበት ሚና ምን ይመስላል? እስካሁንስ ይህ ሚናዉ ታይቷል ወይ? መሰል የአስተዳደር መዋቅር ያላቸዉ ሀገራት ተሞክሮስ?
በተደጋጋሚ እንደሚባለዉ በኢትዮጵያ ሕገመንግስት መሠረት ፕሬዝደንቱ ያለዉ ስልጣን ወጋዊ፣ ሥርዓታዊ ወይም ተምሳሌታዊ ነዉ ይባላል፤ ምን ማለት ነዉ?
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ

dw.de

No comments:

Post a Comment