Saturday, October 26, 2013

ሁለት አሜሪካዊያን መርከበኞች በናይጄሪያ የባህር ዳርቻ በወንበዴዎች ታገቱ

ሁለት አሜሪካዊያን መርከበኞች በናይጄሪያ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ወንበዴዎች ታገቱ።
ወንበዴዎቹ በመርከቧ ላይ በሰነዘሩት ጥቃት ቀድመው ንብረትነቷ የአሜሪካ የሆነችውን መርከብና 11 ተጨማሪ መርከበኞችንም አግተው የነበረ ቢሆንም ፤ ወዲያውኑ መልቀቃቸው ተሰምቷል።
ወንበዴዎቹ አግተዋቸዋል የተባሉትን ሁለት መርከበኞችን ግን ወደ ናይጄሪያ የባህር ዳርቻዎች ወስደዋቸዋል።
መረጃው የደረሰው የናይጄሪያ የባህር ሃይልም ታጋቾችን ለማዳን ሃይሉን ወደ ስፍራው እንዲሰማራ ነው ትእዛዝ ያስተላለፈው።
ምንጭ: አሶሽየትድ ፕሬስ

 https://freedom4ethiopian.wordpress.com/2013/10/26/324-8/

No comments:

Post a Comment