Wednesday, October 9, 2013

ጌታነህ ከበደ በእሁዱ ጨዋታ አይሰለፍም

ጌታነህ ከበደ በእሁዱ ጨዋታ አይሰለፍም

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 28 ፣ 2006 )የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እሁድ ከናይጄሪያ አቻው ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ላይ ጌታነህ ከበደ እንደማይሰለፍ የዋልያዎቹ ምክትል አሰልጣኝ አቶ ታረቀኝ አሰፋ  ገለፁ ።
ምክትል አሰልጣኙ ለፋና  ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት ፥ ለደቡብ አፍሪካው ቢድ ቪስት ዊትስ የሚጫወተው ጌታነህ ከበደ ለክለቡ ሲጫወት ካጋጠመው ጉዳት ባለማገገሙ ነው በጨዋታው የማይሰለፈው ።
ጌታነህ በመብራት ሀይል ሜዳ ልምምዱን እያደረገ የሚገኘውን ብሄራዊ ቡድን ለመቀላቀል ዛሬ በስፍራው ቢገኝም በህመም  ምክንያት ዋልያዎቹን መቀላቀል አልቻለም ።
በውጭ ሀገራት ለተለያዩ ክለቦች እየተጫወቱ የሚገኙት አዲስ ህንጻ ፣ ሽመልስ በቀለ እና ሳላሃዲን ሰኢድ ግን ብሄራዊ ቡድኑን ተቀላቅለው ልምምድ የጀመሩ ሲሆን ፥ በእሁዱ ወሳኝ ጨዋታም የሚሰለፉ ይሆናል ።
በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሳላሃን ሰዒድ በእሁዱ ጨዋታ አይሰለፍም በሚል የወጣው ዜናም ከእውነት  የራቀ መሆኑን  ምክትል አሰልጣኙ አረጋግጠዋል ።

 https://freedom4ethiopian.wordpress.com/2013/10/09/3412/

No comments:

Post a Comment